ኤርምያስ 47

ስለ ፍልስጥኤማውያን የተነገረ መልእክት

1 ፈርዖን ጋዛን ድል ከማድረጉ በፊት፣ ስለ ፍልስጥኤማውያን ወደ ነቢዩ ወደ ኤርምያስ የመጣውየእግዚአብሔርቃል ይህ ነው፤

2 እግዚአብሔርእንዲህ ይላል፤

“እነሆ፤ በሰሜን በኩል ውሃ እየሞላ ነው፣

ኀይለኛ ጐርፍ ይሆናል፤

አገሪቷንና በውስጧ ያሉትንም ሁሉ፣

ከተሞቿንና ነዋሪዎቻቸውን ያጥለቀልቃል።

ሕዝቡም ድምፁን ከፍ አድርጎ ይጮኻል፤

የምድሪቱ ነዋሪ ሁሉ ዋይ ዋይ ይላል፤

3 ከፈረስ ኮቴ ድምፅ፣

ከጠላት ሠረገላ ጩኸትና፣

ከሠረገላው ሽክርክሪት ፍትጊያ ድምፅ የተነሣ፣

አባቶች ልጆቻቸውን ለመርዳት ወደ ኋላ መለስ አይሉም፤

እጃቸውም ስንኩል ይሆናል።

4 ፍልስጥኤማውያንን ሁሉ ለማጥፋት፣

ተርፈውም የሚረዷቸውን ሁሉ፣

ከጢሮስና ከሲዶና ለመቍረጥ፣

ቀኑ ደርሶአልና።

እግዚአብሔርበከፍቶርዳርቻ የቀሩትን፣ ፍልስጥኤማውያንን ሊያጠፋ

ተነሥቶአል።

5 ጋዛ በማዘን ራሷን ትላጫለች፣

አስቀሎና አፏን ትይዛለች።

በሜዳማ ስፍራ የምትገኙ ትሩፋን ሆይ፤

እስከ መቼ ሰውነታችሁን ትቧጥጣላችሁ?

6 “ ‘የእግዚአብሔርሰይፍ ሆይ፤

የማታርፈው እስከ መቼ ነው?

ወደ ሰገባህ ተመልሰህ ግባ፤

ጸጥ ብለህ ተቀመጥ’ ትላላችሁ።

7 ነገር ግንእግዚአብሔርአስቀሎናንና የባሕሩን ዳርቻ፣

እንዲወጋ ሲያዝዘው፣

እንዲፈጽመውም ትእዛዝ ሲሰጠው፣

እንዴት ማረፍ ይችላል?”

Leave a Comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *