በግብጽ ለሚደገፉ ወዮውላቸው
1 ወደ እስራኤል ቅዱስ ለማይመለከቱ፣
ከእግዚአብሔርምርዳታን ለማይሹ፣
ነገር ግን፤ ለርዳታ ብለው ወደ ግብፅ ለሚወርዱ፣
በፈረሶች ለሚታመኑ፣
በሠረገሎቻቸው ብዛት፣
በፈረሶቻቸውም ታላቅ ብርታት ለሚመኩ ወዮላቸው!
2 እርሱም ግን ጠቢብ ነው፤ ጥፋትን ያመጣል፤
ቃሉን አያጥፍም።
በክፉ አድራጊዎች ቤት ላይ፣
በደለኞችንም በሚረዱ ላይ ይነሣል።
3 ግብፃውያን ሰዎች እንጂ አምላክ አይደሉም፤
ፈረሶቻቸውም ሥጋ እንጂ መንፈስ አይደሉም፤
እግዚአብሔርእጁን ሲዘረጋ፣
ርዳታ ሰጪው ይሰናከላል፤
ተረጂውም ይወድቃል፤
ሁለቱም በአንድ ላይ ይጠፋሉ።
4 እግዚአብሔርእንዲህ ብሎኛል፤
“አንበሳ ወይም የአንበሳ ደቦል
የሰበረውን ይዞ ሲያገሣ፣
ብዙ እረኞች
ተጠራርተው ሲመጡበት፣
ጩኸታቸው እንደማያስፈራው፣
በድምፃቸውም እንደማይታወክ፣
የሰራዊት ጌታእግዚአብሔር፣
በጽዮን ተራራና በከፍታዎቿ ላይ ለውጊያ እንዲሁ ይወርዳል።
5 በዐናት ላይ እንደሚያንዣብቡ ወፎች፣
የሰራዊት ጌታእግዚአብሔርኢየሩሳሌምን እንዲሁ ይጋርዳታል፤
ይከልላታል፤ ይታደጋታል፤
በላይዋ ያልፋል፤ ያድናታልም።”
6 እናንተ እስራኤላውያን ሆይ፤ እጅግ ወዳ መፃችሁበት ወደ እርሱ ተመለሱ።
7 በዚያን ቀን በኀጢአት የተሞላ እጃችሁ የሠራቸውን የወርቅና የብር ጣዖቶች ሁላችሁም ትጥላላችሁና።
8 “አሦር የሰው ባልሆነ ሰይፍ ይወድቃል፤
የሥጋ ለባሽ ያልሆነም ሰይፍ ይበላዋል።
ከሰይፍ ፊት ይሸሻል፤
ጐልማሶቹም የግዳጅ ሥራ ይሠራሉ።
9 ጠንካራ ምሽጉ በሽብር ምክንያት ይወድቃል፤
መሪዎቹም የጦር ዐርማ ሲያዩ
በድንጋጤ ይዋጣሉ”
ይላል እሳቱ በጽዮን፣
ማንደጃውም በኢየሩሳሌም የሆነእግዚአብሔር።