መዝሙር 4
የሠርክ ጸሎት ለመዘምራን አለቃ፤ በበገናዎች የሚዜም የዳዊት መዝሙር 1 የጽድቄ አምላክ ሆይ፤ በጠራሁህ ጊዜ መልስልኝ፤ ከጭንቀቴ አሳርፈኝ፤ ማረኝ፤ ጸሎቴንም ስማ። 2 ሰዎች ሆይ፤ እስከ መቼ ድረስ ክብሬን ዝቅታደርጋላችሁ? እስከ መቼስ ድረስ ከንቱ ነገርን ትወዳላችሁ? ሐሰትንስትሻላችሁ?ሴላ…
የሠርክ ጸሎት ለመዘምራን አለቃ፤ በበገናዎች የሚዜም የዳዊት መዝሙር 1 የጽድቄ አምላክ ሆይ፤ በጠራሁህ ጊዜ መልስልኝ፤ ከጭንቀቴ አሳርፈኝ፤ ማረኝ፤ ጸሎቴንም ስማ። 2 ሰዎች ሆይ፤ እስከ መቼ ድረስ ክብሬን ዝቅታደርጋላችሁ? እስከ መቼስ ድረስ ከንቱ ነገርን ትወዳላችሁ? ሐሰትንስትሻላችሁ?ሴላ…
የጧት ጸሎት ለመዘምራን አለቃ፤ በዋሽንት የሚዘመር፣ የዳዊት መዝሙር 1 እግዚአብሔርሆይ፤ ቃሌን አድምጥ፤ መቃተቴንም ቸል አትበል። 2 ንጉሤና አምላኬ ሆይ፤ ወደ አንተ እጸልያለሁና፣ ድረስልኝ ብዬ ስጮህ ስማኝ። 3 እግዚአብሔርሆይ፤ በማለዳ ድምፄን ትሰማለህ፤ በማለዳ ልመናዬን በፊትህ አቀርባለሁ፤…
በጭንቅ ጊዜ የቀረበ ጸሎት ለመዘምራን አለቃ፤ በበገናዎች የሚዘመር፤ የዳዊት መዝሙር በሸሚኒት 1 እግዚአብሔርሆይ፤ በቍጣህ አትገሥጸኝ፤ በመዓትህም አትቅጣኝ። 2 እግዚአብሔርሆይ፤ ዐቅመ ቢስ ነኝና ማረኝ፤ እግዚአብሔርሆይ፤ ዐጥንቶቼ ተናግተዋልና ፈውሰኝ። 3 ነፍሴ እጅግ ታውካለች፤ እስከ መቼ፤ አንተእግዚአብሔርሆይ፤ ይህ…
በስደት ጊዜ የጻድቁ ሰው ጸሎት ዳዊት በብንያማዊው በኩዝ ምክንያት ለእግዚአብሔር የዘመረው መዝሙር 1 እግዚአብሔርአምላኬ ሆይ፤ አንተ መሸሸጊያዬ ነህ፤ ከሚያሳድዱኝ ሁሉ አድነኝ፤ ታደገኝም፤ 2 አለበለዚያ እንደ አንበሳ ይዘነጣጥሉኛል፤ የሚያድነኝ በሌለበትም ይቦጫጭቁኛል። 3 እግዚአብሔርአምላኬ ሆይ፤ ይህን አድርጌ…
የፈጣሪ ግርማ በፍጥረቱ ላይ ለመዘምራን አለቃ፣ በዋሽንት የሚዜም፤ የዳዊት መዝሙር 1 እግዚአብሔርአምላካችን ሆይ፤ ስምህ በምድር ሁሉ ላይ ምንኛ ግርማዊ ነው! ክብርህ ከሰማያት በላይ፣ ከፍ ከፍ ብሎአል። 2 ከልጆችና ጡት ከሚጠቡ ሕፃናት አፍ፣ ምስጋናንአዘጋጀህ፤ ከጠላትህ የተነሣ፣…
በክፉ ላይ ፍርድ ለመዘምራን አለቃ፤ በሙትላቤን ቅኝት፤ የዳዊት መዝሙር 1 እግዚአብሔርሆይ፤ በፍጹም ልቤ አመሰግንሃለሁ፤ ስለ ድንቅ ሥራዎችህም ሁሉ እናገራለሁ። 2 በአንተ ደስ ይለኛል፤ ሐሤትም አደርጋለሁ፤ ልዑል ሆይ፤ ስምህን በመዝሙር እወድሳለሁ። 3 ጠላቶቼ ወደ ኋላ በተመለሱ…
ለፍትሕ የቀረበ ልመና 1 እግዚአብሔርሆይ፤ ለምን እንዲህ ርቀህ ቆምህ? በመከራ ጊዜስ ለምን ድምፅህን አጠፋህ? 2 ክፉዎች የተጨነቀውን በእብሪት ያሳድዳሉ፤ በወጠኑት ተንኰል ይጠመዱ። 3 ክፉ ሰው በልቡ ምኞት ይኵራራል፤ ስግብግቡን ይባርካል፤እግዚአብሔርንምይዳፈራል። 4 ክፉ ሰው ከትዕቢቱ የተነሣ…
የጻድቃን ትምክሕት ለመዘምራን አለቃ፤ የዳዊት መዝሙር 1 በእግዚአብሔርታምኛለሁ፤ ታዲያ ነፍሴን፣ “እንደ ወፍ ወደ ተራራ ብረሪ” ለምን ትሏታላችሁ? 2 ደግሞም ለምን እንዲህ ትሉኛላችሁ? “ክፉዎች፣ እነሆ፣ ቀስታቸውን ገትረዋል፤ የቅኑን ሰው ልብ በጨለማ ለመንደፍ፣ ፍላጻቸውን በአውታሩ ላይ ደግነዋል።…
ከክፉ ዓለም ለመዳን የቀረበ ጸሎት ለመዘምራን አለቃ፤ በስምንተኛው ቅኝት የሚዘመር፤ የዳዊት መዝሙር። 1 እግዚአብሔር ሆይ፤ ደግ ሰው የለምና አንተው ድረስልኝ! ከሰዎችም መካከል አንድ ታማኝ አይገኝም። 2 እርስ በርሳቸው ውሸት ይነጋገራሉ፤ በሽንገላ ከንፈርና በሁለት ልብ ይናገራሉ፤…
በአምላኩ የታመነ ሰው አቤቱታ ለመዘምራን አለቃ፤ የዳዊት መዝሙር። 1 እግዚአብሔርሆይ፤ እስከ መቼ ድረስ ለዘላለሙ ትረሳኛለህ? ፊትህንስ ከእኔ የምትሰውረው እስከ መቼ ድረስ ነው? 2 ከሐሳቤ ጋር የምሟገተው፣ ልቤም ቀኑን ሙሉ የሚያዝነው እስከ መቼ ነው? ጠላቴስ በእኔ…