ማቴዎስ 3

የመጥምቁ ዮሐንስ ስብከት 1 በዚያን ወራት መጥምቁ ዮሐንስ በይሁዳ ምድረ በዳ እየሰበከ መጣ። 2 ስብከቱም፣ “መንግሥተ ሰማያት ቀርባለችና ንስሓ ግቡ” የሚል ነበር። 3 በነቢዩ በኢሳይያስ እንዲህ ተብሎ የተነገረለት እርሱ ነው፤ “በምድረ በዳ፣ ‘የጌታን መንገድ አዘጋጁ፤…

ማቴዎስ 4

የኢየሱስ መፈተን 1 ከዚህ በኋላ መንፈስ ቅዱስ ኢየሱስን በዲያብሎስ ይፈተን ዘንድ ወደ ምድረ በዳ ወሰደው። 2 አርባ ቀንና አርባ ሌሊት ከጾመ በኋላ ተራበ። 3 ፈታኙም ወደ ኢየሱስ ቀርቦ፣ “የእግዚአብሔር ልጅ ከሆንህ እነዚህን ድንጋዮች እንጀራ እንዲሆኑ…

ማቴዎስ 5

የተራራው ስብከት 1 ብዙ ሕዝብ እንደ ተሰበሰበ ባየ ጊዜ፣ ወደ ተራራ ወጣና ተቀመጠ፤ ደቀ መዛሙርቱም ወደ እርሱ መጡ። 2 እንዲህም እያለ ያስተምራቸው ጀመር፤ 3 “በመንፈስ ድኾች የሆኑ ብፁዓን ናቸው፤ መንግሥተ ሰማይ የእነርሱ ናትና። 4 የሚያዝኑ…

ማቴዎስ 6

ስለ ምጽዋት አሰጣጥ 1 “ሰዎች እንዲያዩላችሁ፣ መልካም ሥራችሁን በፊታቸው ከማድረግ ተጠንቀቁ፤ እንዲህ ካደረጋችሁ ከሰማዩ አባታችሁ ዋጋ አታገኙም። 2 “ግብዞች በሰዎች ዘንድ ለመከበር ብለው በየጎዳናውና በየምኵራቡ እንደሚያደርጉት፣ አንተም ለድኾች ምጽዋት በምትሰጥበት ጊዜ ይታይልኝ ብለህ ጥሩምባ አታስነፋ፤…

ማቴዎስ 7

በሌሎች ላይ አለመፍረድ 1 “እንዳይፈረድባችሁ በማንም ሰው ላይ አትፍረዱ፤ 2 በምትፈርዱበትም ዐይነት ይፈረድባችኋል፤ በምትሰፍሩበትም መስፈሪያ ይሰፈርላችኋል። 3 “በዐይንህ ውስጥ ያለውን ግንድ ሳትመለከት፣ በወንድምህ ዐይን ያለውን ጕድፍ ለምን ታያለህ? 4 በዐይንህ ውስጥ ግንድ እያለ ወንድምህን፣ ‘ዐይንህ…

ማቴዎስ 8

የለምጻሙ መንጻት 1 ከተራራው በወረደ ጊዜም ብዙ ሕዝብ ተከተለው። 2 እነሆ፤ አንድ ለምጻምሰው ወደ ኢየሱስ ቀረበና ከፊቱ ተንበርክኮ እየሰገደለት፣ “ጌታ ሆይ፤ ብትፈቅድስ ልታነጻኝ ትችላለህ” አለው። 3 ኢየሱስም እጁን ዘርግቶ ዳሰሰውና፣“ፈቃዴ ነው፤ ንጻ!”አለው። ሰውየውም ወዲያውኑ ከለምጹ…

ማቴዎስ 9

የሽባው ሰው መፈወስ 1 ከዚህ በኋላ ኢየሱስ ባሕሩን በጀልባ ተሻግሮ ወደ ራሱ ከተማ መጣ። 2 በዚያም ሰዎች አንድ ሽባ ሰው በቃሬዛ ተሸክመው ወደ እርሱ አመጡ። ኢየሱስም እምነታቸውን አይቶ ሽባውን፣“አይዞህ አንተ ልጅ፤ ኀጢአትህ ተሰርዮልሃል”አለው። 3 በዚህን…

ማቴዎስ 10

የዐሥራ ሁለቱ ደቀ መዛሙርት መላክ 1 ኢየሱስ ዐሥራ ሁለቱን ደቀ መዛሙርት ወደ እርሱ ጠርቶ ርኵሳን መናፍስትን እንዲያወጡ፣ ደዌንና ሕማምን ሁሉ እንዲፈውሱ ሥልጣንን ሰጣቸው። 2 የዐሥራ ሁለቱ ሐዋርያት ስም የሚከተለው ነው፦ መጀመሪያ ጴጥሮስ የተባለው ስምዖንና ወንድሙ…

ማቴዎስ 11

መጥምቁ ዮሐንስ ወደ ኢየሱስ የላከው ጥያቄ 1 ኢየሱስ ለዐሥራ ሁለቱ ደቀ መዛሙርቱ ትእዛዙን ሰጥቶ ከጨረሰ በኋላ ለማስተማርና ለመስበክ ወደ ገሊላ ከተሞችሄደ። 2 ዮሐንስ በእስር ቤት ሆኖ ክርስቶስ በማድረግ ላይ ያለውን ነገር በሰማ ጊዜ፣ ደቀ መዛሙርቱን…

ማቴዎስ 12

ሰንበትን ስለ ማክበር 1 ከዚህ በኋላ ኢየሱስ በሰንበት ቀን በእህል ዕርሻ ውስጥ አለፈ፤ ደቀ መዛሙርቱም ስለ ራባቸው እሸት ቀጥፈው ይበሉ ጀመር። 2 ፈሪሳውያንም ይህን አይተው፣ “እነሆ፣ ደቀ መዛሙርትህ በሰንበት ቀን መደረግ የሌለበትን እያደረጉ ነው” አሉት።…